ድንገት የእሳት ቃጠሎ ለደረሰበት ሰው መድረግ ያለበት የመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ
• የእሳት ቃጠሎ አደጋ የደረሰበትን ሰው በአፋጣኝ ከቃጠሎው ቦታ ማራቅ • በጣም ያለቀዘቀዘ ወይንም በረዶ ያልሆነ ውሃን በተቃጠለው አካል ላይ ማደረግ ምክንያቱም በረዶ ቃጠሎ የደረሰበትን ቆዳችንን ስለሚጎዳ ነው። • ማንኛውንም ልብስ ወይም ጌጣጌጥ አደጋው ከደረሰበት ሰው ላይ ማውለቅ፥ ነገር ግን ከቆዳ ጋር ተጣብቆ ያለ ማንኛውንም ነገር ለማንሳት መሞከር ለመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ ተገቢ አይደለም፡፡ • አደጋው የደረሰበት ሰው በብርድ እንዳይጠቃ መከላከል • የህመም ማስታገሻ መድሀኒቶች በአቅራቢያ ካገኙ መስጠት • በአፋጣኝ ወደ ህክምና ቦታ መውሰድ ናቸው።