ፈዴራል ፖሊስ በሃዋሳ ከተማ ወልደ ኣማኑኤል ጎዳና ላይ ሰላማዊ ሰዎችን ስደበድብ ኣመሽ


በዛሬ ቀን በሃዋሳ ከተማ በተለምዶ ወልደ ኣማኑኤል ሃውልት ኣካባቢ ካለው ኣንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ በጊዜያዊ ካምፒነት ተከራይተው የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ ኣባላት በኣካባቢው በመንገድ ላይ ሲጓዙ የነበሩትን  የሲዳማን ተማሪዎች በመደብደባቸው የኣካባቢው ነዋሪዎች ድርጊቱን በመቃዎወም ተቃውሞኣቸውን ድንጋይ በመወርወር ስገልጹ ማምሸታቸው ተገለጸ።

ከኣከባቢው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ከሆነ፤ የሲዳማ የክልል ጥያቄን ተከትለው በኣካባቢው የሰፈሩት እና በተለይ ሲዳማውን በክፉ ኣይን ስከታተሉ የነበሩት የፈደራል ፖሊስ ኣባላት ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት መንገድ ላይ የነበሩትን ተማሪዎች ደብድበው ለሆስፒታል እና ለሞት ዳርጓዋል።

ከተደበደቡ ተማሪዎቹ መካከል ከዎንሾ ወረዳ የመጣ ኣብረሃም የተባለው ተማሪ ኣንዱ ሲሆን በከፍተኛ ደረጃ ከተደበደበ በሃላ በኣንድ ፈዴራል ፖሊስ ተገድሏል የሚል ወሬ በመነፈስ ላይ ነው።


በተጨማሪም ተማሪዎቹ ለምን ይደበደባሉ በማለት የተቃዎሙ ሰዎችም ራሳቸው በፈዴራል ፖሊስ በኣሰቃቂ ሁኔታ የተደበደቡ ሲሆን ከነዚሁ ሰዎች መካከል ሁለቱ ሆስፒታል መግባታቸው እየተነገረ  ነው።


በጉዳዩ ላይ ማረጋገጫ ብሎም ዝርዝር መረጃ እንደደረደን እናቀርባለን።

ከክስተቱ ጋር በተያያዘ መረጃው ያላችሁ ሰዎች በዚህ ኢሜል መልእክቶቻችሁን ልትልኩልን ትችላላችሁ: nomonanoto@gmail.com





Comments

Popular posts from this blog

ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ከተፅዕኖ ነፃ ሳይሆን የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ማውጣቱን ተቃወመ

የሐዋሳ ሐይቅ ትሩፋት

በሲዳማ ክልል የትግራይ ተወላጆች ምክክር